1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሲናይ በረኃ የታገቱት ኤርትራውያን ስደተኞች ጉዳይ

ሐሙስ፣ ኅዳር 30 2003

ሁለት መቶ ሀምሳ የሚሆኑ የኤርትራ ስደተኞች ሲናይ በረሃ ውስጥ ሳይታገቱ እንዳልቀረ ተሰማ።

https://p.dw.com/p/QURA
ምስል DW

የግብጽ መንግስት ይህንኑ ጉዳይ ማጣራት መጀመሩን አመልክቶዋል። ስደተኞቹ የት እንዳሉ በግልጽ አለመታወቁና በአጋቾቻቸውም በደል እየደረሰባቸው ነው የመባሉ ነገር እንዳሳሰበው የተመድ የስደተኝ ጉዳይ ተመልካች መስሪያ ቤት አስታውቋል። ስለነዚሁ ስደተኞች ጉዳይ አርያም ተክሌ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂውመን ራይትስ ዎች የግብጽ ጉዳይ ተመራማሪ ወይዘሮ ሄባ ሞራየፍን አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች።

አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ