1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሊባኖስ የውጭ ሀገራት ዜጎች ላይ የሚፈጸም የመብት ጥሰት

ሰኞ፣ መስከረም 10 2003

ሂውማን ራይትስ ዎች ሊባኖስን ወቀሰ።በውጭ ሀገራት የቤት ሰራተኞች ላይ የሚደርሰውን ጥቃርና በደል አላስቆመችም ብሏል።

https://p.dw.com/p/PHgu
ኢትዮዽያዊት በሊባኖስምስል AP

ዓለም ዓቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዎች ሊባኖስን የወቀሰበትን መግለጪያ አውጥቷል። በቤት ሰራተኝነት የሚሰሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች መብቶች አይከበርም ሲል ድርጅቱ ሊባኖስን የከሰሰበት መግለጪያ የወጣው ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ ነው። የውጭ ሀገራት ዜጎች በአሰሪዎቻቸው ወይም በቀጣሪዎቻቸው የሚደርስባቸው ጥቃትና የመብት ጥሰት እየጨመረ መጥቷል። የሊባኖስ መንግስት የወሰደው እርምጃ የለም ሲል ሂውማን ራይትስ ዎች ከሷል። ኢንዲ አክት የተሰኘ በዘረኝነት ላይ የሚሰራ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የሂውማን ራይትስ ዎችን መግለጪያ የሚደገፍ ብሎታል። በድርጅቱ የሊባኖስ ቅርንጫፍ የኮሚኒኬሽን ባለሙያን ሂሩት መለሰ አነጋግራ ተከታዩን ዘገባ አዘጋጅታለች።

መሳይ መኮንን

ሒሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ